image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ህዝባዊ የዉይይት መድረክ ተካሔደ።

ህዳር 14, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ቃል የሕዝባዊ የውይይት መድረክ በዛሬዉ እለት ተካሔዷል። በወረዳዉ በተካሔደው የውይይት መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል። የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ቱሩፋት በሚል ርዕስ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሕዝብ መድረኮች ላይ ከነዋሪዎቻችን ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ቅሬታዎች እና አስተያየቶች በተግባር የተሰጡ ምላሾች፣ እንዲሁም ቀሪ ሥራዎችን አስመልክቶ በወረዳዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ በአቶ ደረጄ ፈይሳ በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 በተካሔደው የህዝብ የውይይት መድረክ አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ የአዲስ አበባ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዳይሬክተር ፣ወ/ሮ ተስፋነሽ ጋሻው የክፍለ ከተማው ንግድ ፅ/ቤት ሀላፊና የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ በጋራ መርተውታል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማችን በተለያዩ የልማት ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶች የተመዘገቡት መንግሥትና ሕዝብ አንድ ሆነው በመቀናጀትና በመናበብ ሊፈጽሟቸው በመቻላቸው መሆኑን በውይይቱ ተብራርቷል። በውይይቱ በመንግሥትና በሕዝብ ትብብር የተሰሩ በርካታ ሥራዎችን እና የተመዘገቡ ውጤቶችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ እንዲሁም የሕዝብን ተሳትፎ ይበልጥ በሚያረጋግጡ ቀጣይ የጋራ ዕቅዶች ላይ ዳር ማድረስ እንደሚደሚባ መግባባት ተፈጥሯል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች